Tuesday, January 15, 2019

ፍ ቅ ር … የ መ ኖ ር ተ ስ ፋ

ፍቅር … የመኖር ተስፋ
#ሳteናw
ቴዲ ያቀነቅናል…
አይኖቼ አያዩ ብርሃን የላቸው፣በልጅነቴ ድሮ አጥቻቸው፣
ልቤን ተሰማው እንግዳ ነገር፣ምርኩዝ ይዤ ነው የሚውቀው ሀገር።
አለም ታየችኝ ባንቺ ውስጥ ሆና፣ በፍቅር ኩራዝ በላንባዲና።

ቴዲ ልክ ነው፣ ፍቅርን ብርሃን ፈንጣቂ ላንባዲና አድርጎ ማቀንቀኑ ስሜት የሚሰጥ ነው። በተለይ ከኔ ህይወት ጋር… በሚገባ ይጣጣማል የቴዲ ላንባዲና። ይኸው ሙዚቃ  በህይወቴ ሲተነተን ተከታዩን ምስል ይሰጣል።

እርግጥ ነው፣ በልጅነቴም ሆነ አሁን አይኖች የሌሉኝ አይነስውር አይደለሁም። በአይን የገለፅኳት አሳዳጊ አያቴን ነው። አስተዳደጌ በአያቴ እጅ ነበር። እና አአያቴ አይኖቼ ነበረች ብል ዝያጋነንኩ እንዳይመስልህ፣ (ከመሰለህም ሂድበት)። በመሆኑም በአያቴ እጅ ማደጌ፣ ወሰኑን ያለፈ እንክብካቤ እና ፣ ፍቅር እንደ አይን ሆኖኛል። እኔ ልብ ያላልኩትን እንቅፋት፣ ችግር አደጋ…  በአያቴ ተንከባካቢ አይን ይገባና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ከአያቴ ይሰጠኛል። እንቅፋቴን ይጠረግልኛል።ችግሮቼን በአያቴ የፍቅር አይን ይወገድልኛል። ካንዣበብኝ አደጋ ይጠብቀኛል። አይን የሆነኝ የአያቴ ፍቅር ብዙ መልካም ነገሮች እዲገጥሙኝ ሆኗል። አያቴ ይህን በነበረን አጭር የህይወት ቆይታ በሚገባ  አለማምዳኛለች። ነገር ግን ላታዛልቀኝ በልጅነቴ ጥላኝ ወደሌላው አለም ነክታዋለች። በልጅነቴ ፍቅሬን አይኔን አጣሁት። አያቴን።

ቴዲ ይቀጥላል …

የአያቴን የፍቅር አይኖቼን በልጅነቴ ማጣቴ ያልተረጋጋ ህይወት እንድመራ ሆንኩ።  ከሌላው ቤተሰብ ጋር ህይወቴ ቢቀጥልም እንደ አያቴ አይኔ መሆን አልቻሉም።  የአያቴን እንክብካቤ ከሌሎቹ ቤተሰቦቼ ማግኘት አልቻልኩም። አያቴ አይታ ትሸፍንልኝ የነበረውን ክፍተት የሚያከናንበው ጠፋ። ይህ ክፉ ልማድ ዘያቴን ካጣሁ ቡሃላ ለማህበራዊ ህይወቴ እንደግርዶሽ ሆኖ በአቅራቢያዬ የሚገኙ መልካም ነገሮችን ጋረደኝ። የባይተዋር፣ የግድ የለሽ፣ ቀቢፀ ተስፋ የህይወቴ እርምጃ ምርኩዜ ሆነ። ይህም ለብዙ ታዛቢ የሚያስታውቅ ምልክት አሳየ ፣ ምክኒያቱም ከአይኖቼ መጥፋት ቡሃላ(ከአያቴ ሞት) ምርኩዜ የሆኑት፣ባይተዋርነትና፣ ቀቢፀ ተስፋዎቼ በግልፅ ያስታውቁብኝ ነበሩ። ልቤን ደስታ ተሰማው። ከመሬት ተነስቶ አልነበረም። በህይወት አጋጣሚ፣  ተላመድኩ። ተዋደድኩ። ተፋቀርኩ። ብቸኝነቴን፣ ባይተዋርነቴን በርሷ ፍቅር አሸነፍኩ፣ ተስፋ አልባነቴን ከሷ ጋር ወደፊት በሚኖረኝ ተስፋ ሞላው። ለተመልካች አስገራሚ ለውጥ አሳየው።

የመኖር ትርጉሞቼ በፍቅር ሰበብ ታዩኝ፣ አላማና ስኬቴ
ይገለፁልኝ ጀመር። ከዚህ ቀደም ባህሪዬ የነበረው ግድ የለሽነት፣ ደብዛው ጠፍቶ ለህይወቴ ግድ መስጠት ግድ አለኝ። በስራዬ ቀልጣፋና፣ በሀይማኖቶ ደህና፣ በማህበራዊ ህይወቴ ንቁ እሆን ገባው፣ የከበበኝ ፅልመት በፍቅር ብርሃን ተገፈፈ። ይህን ለውጤን ያየ የሚያወወቀኝ ሁሉ በግርምት ለፈለፈ። ፍቅር ለምባዲና ሆኖ አለምን አሳየኝ። የፆታ ፍቀር ብቻ አይደለም። ከዚህ ቀደም በፅልመቴ ሳቢያ ትኩረት የነፈኳቸውን  ዘሪያ ገቤ ያሉ መልካም ነገሮች አይቼ አንዳፈቅር ሆንኩ ፣ ለሀገሬ፣ለቤተሰቤ፣ አፀፋዊ ፍቅር ባገኝም ባላገኝም ፍቀር መስጠት እንዳለብኝ ተረዳው፣ እውነተኛ አፍቃሪ ምላሽም ሆነ ምስጋና አይከጅልም። አሁን አየ አይኔ፣ አሁን አየ አይኔ፣ የሚለው የቴዲ ስንኝ በህይወቴ ትርጉም አገኘ።

……
እንደትኮራበት አህንህን ፍቅር ያልነካው ልብህን።
በማየትበ ስለማትበልጠኝ ና መነፅሬን ለውጠኝ።
ፍቅር የለሌለው አይናማ ውጦታልና ጨለማ፣
ሰው ወዶ ሰው ያልወደደው ምርኩዜን መጥቶ ይውሰደው።

ፍቅር መስጠት የማይችል ፍቅር ሊያገኝ አይችልም። ፍቀር ከሌሌ ህይወት ጨለማ ነች የግዞት እስር ቤት ነች። የፍቅርን ሀይል ማወቅ የሚሻ ልቡን ለፍቅር ይክፈት ፣ አለ አይደል ወለለለለል ፣ ነገር።
ፍቅር ብሌን ነው። ፍቅር አይን ነው። ዙሪያ ገብህን የራቀህን ተስፋ የምታይበት መመልከቻ መነፅር ነው።  ፍቅር አጥተህ የታወርክ ካለህ…  የተመልካችነት ስሜት ተሰምቶህ እንዳትኮፈስ፣ ፍቅር አልባ ከሆንክ አምነኝ ታውረሃል፣ ለሀይማኖትህ ፍቅር ከሌለህ፣ በተግባር ያላሳየህ ከሆነ። ሀይማኖተኛ ነኝ የሚል ቃል ትንፍሽ አንዳትል!! በጭራሽ እንዳይዋጣህ!!  ለሀገርህ ያለህ ስሜት፣ የሟሸሸ ከሆነ፣ የተስፋ አይታይህም። ተስፋህ አየር  ላይ አልያም  በፍቀር የመጣ ህይወቴ ተቀይራለችና፣ በተስፋ ሙላት ተሞልታለችና፣ ለሀይማኖት፣ ለቤተሰብ፣ ለህዝቤ፣ ለሀገሬ ፍቅ ር እንዲኖረኝ ገርቶኛልና፣ ልምዴን ተቀበል፣ እንካ መነፅሬን ውሰድና፣ ፍቅር ልበስበት። በጎ በጎውን ተመልከትበት። ሰበብ ሊሆንህ ይችላል። የሀገር ፍቅር ከመሬት ተነስቶ አይገኝምና የኔ ምክር መንገዱን ያሰፋልህ ይሆናል። በፖለቲካና በአስተዳደር የመጣ ያጣኸውን የሀገር ፍቅር ስሜት፣ ዞር ብለህ በፍቅር መነፅር ሚስኪንወገንህን ተመልከት። የዛኔ በሀገር ፍቅር መንፈስ ትሞላለህ። አንድነትን ታጠናክራራልህ። ለመጥላት ሰበብ የሆነህን ሁኔታ በአንድነት ፍቅር ትደመስሳለህ። የዛኔ ልክ እንደኔው አሁን አየ አይኔን በስሜት ታቀነቅነቀለህ።
ወገሬት!!