Sunday, August 26, 2018

አ ሰ ብ ት መ ለ ስ ል ን

"አሰብ ትመለስልን "
#ሳteናw

… እኛ ኢትዮጲያዊያን ከሶስት አስርት አመታት በፊት ከ1500 ኪሜ በላይ የሚረዝም የባህር በር እንዳልነበረን ሁሉ፣ ዛሬ ላይ በታሪካዊ ስህተት የባህር በር የማጣታችን ነገር ፣ እንደ አንዳች ነገር ይከነክነኛል፣ ይቆጨኛል፣…  በተለይ በተለይ ለወደብ ሲሉ ደማቸውን የገበሩ ጀግና አባቶቻችንን ሳስብ… ሲያልፍም ሀገሬ በየቀኑ ለወደብ ኪራይ  የምታወጣው ሚሊዮን ዶላሮች፣ እንደቀልድ ያጣነው የባህር በር ኖሮ ቢሆንና ፣ ይህ ለሀገር ውስጥ ልማት ቢውሉ ኖሮ ብዬ ሳስብ። ያሰላም እርርርር ጭስስስስ!!

ይህንን ስሜት አብዛኛው ኢትዮጲያዊ ወገኔ የሚጋራኝ ይመስለኛል። ለዛሬው የባህር በር ማጣታችን ብዙ ምክኒያቶች መደርደር ቢቻልም፣ በዋናነት ግን በመጨረሻው ዘመን የተደረገው የአልጀርሱ  ስምምነት ይመስለኛል። አዎ በዛ ስምምነት ላይ ኢትዮጲያን "የወከሉት ልኡካን፣ ምን ልኡካን ባንዳ እርግማን ልበላቸው እንጂ!!  በድርድሩ ላይ  ለኢትዮጲያ የባህር በር ማግኘት  ለዘብተኛ አቋም ባይኖራቸው ኖሮ በጊዜው  ከ80 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጲያ የባህር በር የማግኘቷ ዕድል ሰፊ እንደነበር በዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማርያም የተፃፈው አሰብ የማን ናት በሚለው መፅሃፍ በዝርዝር ተቀምጣል።

በመሰረቱ  ወደብ አልባ ያደረገን የአልጀርሱ ስምምነት፣ አፄ ሚኒሊክ በጣልያን ተፅዕኖ እጃቸውን ተጠምዝዘው ፍትሃዊ ባልሆነ መንገድ በተዋዋሉት ውል ተንተርሶ የተደረገ ነው። በመሆኑም የኢትዮጲያን ጥቅም ያስጠበቀ አልነበረም። ይህን ያወቁ የኢትዮጲያ ተዋዋዮች ጠበቆች፣ ምን አይነት የኢትዮጲያዊነት ስሜት እንዳላቸው ግልፅ ባይሆንም ሙሉ በሙሉ ኢትዮጲያን የባህር በር ያለምንም ክርክርና  ይግባኝ አስረክበው እጃቸውን እያጨበጨቡ በኢትዮጲያ ህዝብ ላይ ዘመን አይሽሬ  የበደል በደል የግፍ ግፍ ፈፅመው መጥተዋል።

እርግጥ ነው ከ1500 ኪሎ ሜትር በላይ የነበረው የቀድሞ የኢትዮጲያ የባህር በር ና ቀይ ባህር፣ስትራቴጂክ የሆነ ስፍራ በመሆኑ  በተለያዩ ዘመናትት የውጭ ወራሪዎች በማፈራረቅ ለማስተናገድ ተገዷል። ከወራሪዎቹም  ውስጥ ግብፅ፣ ቱርክ እንግሊዝና ጣልያን በዋናነት ይጠቀሳሉ። ከቅርብ ጊዜ ታሪክ ብንጀምር እንኳ ጣልያን ለ50 አመት፣ እንግሊዝ ለ10 አመት ገዝተዋታል የጥንቷን ሀማሴን የዛሬዋን ኤርትራ!!
ይህም የባንዳ መፈራረቅ በስፍራው ይኖሩ በነበሩ ኢትዮጲያዊያን ላይ የኢትዮጲያዊነት ስሜታቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ መፍጠሩ አልቀረምና የመገንጠል ፅንሰ ሀሳብ ተፀንሶና ተወልዶ እውን መሆኑ አልቀረም።

ሌላው የባህር በር ለማጣታችን ምክንያት አንዱ የአድዋ ጦርነት ነው።

እምዬ ምኒሊክ በአድዋው ድል  ፣ መረብን አለመሻገራች ለተባራሪው ፋሺሽት ጦር ቀይ ባህር ከመስጠም አዳነው። ሃምሳ አመት ከመረብ ማዶ ባለችው የጥንቷ ሐማሴንና፣  ከአንድ አፋራዊ ግለሰብ የተከራያትን አሰብን  ሰፍቶ ኤርትራ የሚል የሚል ስያሜ አውጥቶ፣ ለሃምሳ አመት ቅኝ ገዛ፣ በሃምሳ አመት ውስጥ በራሱ ስዕብና የተገነባ ትውልድ ተፈጠረ። በዚህ ረጅም ዘመን  ያለፈው የአርትራ  የቀድሞው  ትውልድ በኢትዮጲያዊነት ላይ ምንም ጥያቄ ባይኖረውም በአዲሱ ትውልድ ዘንድ ኢትዮጲያዊነቱ መሸርሸሩ አልቀረም። 
አይ እምዬ ሚኒሊክ ምን ነበር  መረብን ተሻገረው ነጫጭባውን መንጋ ቀይ ባህር ባሰመጡልን ኖሮ።

ሌላኛው አመክኒዮ የፌዴሬሽኑ መፍረስ ነው። በአፄ ሃይለስላሴ ዘመን ኤርትራ ከኢትዮጲያ ጋር በፌዴሬሽን እንድተዳደር በአለም መንግስታት ተፈርዶ ፌዴሬሽኑ ተግባር ላይ ቢውልም። የኢትዮጲያዊነት ስሜቱ የሚያይልበት የኤርትራ ህዝብ ግን " ለምን በፌዴሬሽን?  ኤርትራ እንደ አንድ የኢትዮጲያ ክልል ትተዳደር " የሚሉ ጥያቄዎች ማንሳታቸው አልቀረም። በኤርትራ ፓርላማ ኤትዮጲያዊ አንድነት አቋም ባላቸው አባላት የድምፅ ብልጫ፣ ፌዴሬሽኑ እንዲፈርስ ተደረገ።

በዚህ የተቃወሙ ሃይላት፣ በኢትዮጲያ ታሪካዊ ጠላቶች ትብብር ጀብሃ የሚባል ታጣቂ ተፈጠረ። አላማውም ኤርትራን ነፃ አውጥቶ በራሳ የምትተዳደር ሃገር ለመመስረት ነበር። ይህ ድርጅት በሃይለስላሴ መንግስት ላይ የራስ ምታት ሆነ። ጀብሃአብዛኛውንና ቆላ የሙስሊሙን ማህበረሰብ የሚወክል በመሆኑ በደጋውና በክርስትያኑ ህዝብ መካከል ክፍተት ተፈጠረ። ይህንን ክፍተት በመጠቀም የሃይለስላሴ መንግስት ከራሱ ከጀብሃ አባሎች ተገንጥሎ ሻዕቢያ የሚባ ለውን ድርጅት፣ ጀብሃን እንዲያዳክመለት በሚል፣ እንቋቋም ያላሰለሰ ጥረት አደረገ። የአፄው መንግስት ተምኔቱ ሳይሰምር  ቀረ።  ጀብሃን ይሸረሽርልኛል፣ የኢትዮጲያንና የኤርትራን አንድነት  ያስጠብቅልኛል የተባለው ድርጅት ሻዕቢያ፣ ነገሩ ተገላቢጦሽ ሆነና  ለረጅም ዘመናት ለኢትዮጲያ የእሳት አሎሎ ከሆነ ቡሃላ ኤርትራን ከኢትዮጲያ ለመገንጠል፣ በቃ። "አይዋስ ቢዋሰኝ ከባለዕዳ ባሰኝ " ይሉሃለ ይሄ ነው። እነዚህ አመክኒዮዎች እንዳሉ ቢሆንም መግቢያ ላይ በጨረፍታ የተገለጠው  የአልጀርሱ ኢፍትሃዊ ስምምነት ሀገሬን የባህር በር በማሳጣት ረገድ የአንበሳውን ድረሻ ይወስዳል። እንግዲህ የባህር በር ጉዳይ በወፍ በረር ሲቃኝ  ከላይ ያለፈውን ይመስላል።

ያለፈው አልፏል። የአሁኑ ትውልድ ግን በዲፕሎማሲም ሆነ በሌላ መንገድ ኢትዮጲያን የባህር በር እንድታገኝ ያላሰለሰ ጥረት ሊያደርግ ይገባናል፣ አለበለዚያ የባህር በር ላለማጣት የወደቁ የአባቶቹ አጥንት ይፋረደናል!!

ወገሬት!!

" ስ ጋ ት "


#ሳteናw

  በመንደራች ነዋሪዎች ዘንድ እንደ እናት በምትታየው አያቴ ጋር፣ የህልሞችን ፍቺ እየሰማው በማደጌ ነው መሰለኝ ለህልም ያለኝ አመለካከት አዎንታዊ ነው። ለምሳሌ :- አዲስ ጫማ አድርጎ በህልሙ ያየ፣ ሚስት የማግባት መልዕክት። ጥርስ መውለቅ፣ የሚሞት ሰው መኖሩን።… ወርቅ ማድረግ፣ልጅን የማግኘትን። ወዘተ… ከአያቴ  እና ከማህበረሰቤ በተለያዩ ወቅቶች የሰማዋቸው የህልም ፍቺዎች ነበሩ።

  ትልቅ ከሆንኩም ቡሃላ ከሰውም ከራሴም ህልም እንደተረዳሁት ህልም ለሰው ልጅ ቀድሞ የሚተላለፍ መልዕክት ሁላ ይመስለኛል። አንድ ቀን ታላቋ እህቴ የታችኛው ጥርሷ ወልቆ በህልሟ ማየቷን ስትነግረኝ፣ ስለ ህልም ከነበረችኝ ትንሿ ግንዛቤዬ ማንነቷን ያላወኳት ሴት እንደምትሞት ነገርኳት። እንዳልኩትም በሳምነቱ በጣም የምትወዳት ጓደኛዋ ሞተች።
እንደውም የሆነ ጊዜ እኔ እራሴ በህልሜ የታችኛው ጥርስ ሲነቃነቅ በማየቴ፣ ወይ እናቴ ወይ ከእህቶቼ አንዷ ባትሞትም ጤናዋ ላይ እክል እንደሚገጥማት ፍቺውን ለራሴ ሰጥቼ፣ በስጋት አየጠበኩ ነበር። ፍቺውን ልክ ነበርኩ በጥቂት ቀናት ውስጥ ውጪ የነበረችው አንዷ እህቴ ለከፋ አደጋ ያላጋለጣት የመኪና ግጭት ደርሶባት ሆስፒታል ውስጥ እንደሆነች አወኩ። እነዚህና የአያቴ የህልም ፍቺዎች ተደራርበው የህልምን  እውነትነት አረጋግጠውልኛል። ነገርን ነገር ያሳዋል አይደለም ነገሩ፣ ህልም ስል አንድ ድሮ በኢቲቪ  ያየሁት ቀልድ ትዝ አለኝ። ቀልዱ እንዲህ ነው…

ብርቱካን የምትባል ልጃቸውን ያፈቀረው ወጣት  የአይን ፍቅሩን ለማስታገስ ህልም በማስፈታት ሰበብ፣ አርጩሜ ይዘው በር ላይ ከተቀመጡት አባቷ ዘንድ ይቀርብና ህልሙን ይተርክላቸው ጀመር። "ተራራማ ቦታ ይመስለኛል … ወንዝም አለ … ከሱ ለጥቆ የዝሆኖች መንጋ ይታየኛል … ከዝሆኖቹ ማዶ ደግሞ የቆመ ትልቅ ጥቁር ሰውዬ አርጩሜ ይዞ  የብርቱካን ተክል  ሲጠብቅ አየው ሲል … (ብርቱካን የምትለዋን ቃል ጠበቅ አድርጎ) እየተፍለቀለቀ ይነግራቸዋል።
… ግሩም ነው ሲሉ ጀመሩ አዛውንቱ። ግሩም ህልም ነው… እንግዲህ ፍቺው… ብለው አቋረጡና  በመጀመሪያ የደንቧን እስር ብር ብለው እጃቸውን ይዘረጉለታል። አውጥቶ ይሰጣቸዋል። ቀጠሉ አዛውንቱ ያው እንግዲህ ተራራው ተራራ ነው፣ እእእ ወንዙም ወንዝ ነው ብለው ፍቺውን ያበቃሉ። እሺሺሺ አለ፣ ህልሙን እንዲጨርሱለት የጠበቀው ወጣት።  ለቀሪው ህልም ተጨማሪ አስር ብር መክፈል እንዳለበት ያረዱታል። አሱም እያጉረመረመ አስር ብር አውጥቶ ይጨምርላቸዋል።
ከወንዙ ማዶ ያየኸው ዝሆንም አይደል? ዝሆኑም ያው ዝሆን ነው ብለው … ያበቃሉ።  ሌላ ፍቹ ቢጠብቅ፣ አይን አይናቸውን እያየ ቢቁለጨለጭ፣ ጭጭ!!
"እንዴ ምንድነው?" ወጣቱ ብስጭት ይላል በፍቺው።
"ምነው ምን ሆንክ?" አሉት።
"ተራራውም ተራራ ነው! ዝሆኑም ዝሆን ነው! ወንዙም ወንዝ ነው! ምን አይነት የህልም አፈታት ነው?" አሁንንም ንድድ እንዳለው ጠየቃቸው።
"እና እንዴት እንድፈታልህ ነው? የፈለከው? ተራራውን ፣ ሜዳ ነው ልበልህ?  ዝሆኑን ጦጣ ነው ልበልህ? ወንዙን ቀይ ባ ህር ነው ልበልህ?  ሲሉ አፈጠጡበት ከሱ ይበልጥ ግለው። ይሄኔ ዋናውና የመጨረሻው ፍቺ እንዳያመልጠው ሰግቶ በረድ ብሎ ቀጣዩን እንዲፈቱልት በመማፀን ገፅታ ጠየቀ። ሌላ አስርብር ተጠየቀ። ከፈለ። ፍቺው ቀጠለ…
"እንግዲህ የህልሙ አስኳል፣ ጥቁሩ ደውዬና ፣የብርትኳኑ ተክል ነው። ብርቱካኑ የኔ ልጅ ብርቱካን ነች። ጥቁሩ ሰውዬ ደግሞ እኔ ነኝ።
ወጣቱ ያፈቀራት ልጅ ስም በመነሳቱ ሲፍለቀለቅ  … ሽማግሌው ቀጠሉ። ወጣት ህልሙ ተፈታልህ አይደል?  በል ሂድ ብርቱካንን መንካት የለም!! እኔ እዚህ የምጠብቀው እሷኑ መስሎኝ! ብለው በያዙት አርጩሜ ጀርባውን ላጥ፣ ሲያደርጉት ተነስቶ ቅድድ።

  ወደ ዋናው ሀሳቤ ስመለስ፣ ለህልም ካለኝ ጥቂት ልምድና አመለካከት ተጨማምሮ ፣ እጅግ በጣም የምወዳት ጓደኛዬ፣ የጥርስ መውለቋን ህልም አናቱ አንዳየች በጨዋታችን መሃል ነግራኝ ስጋት ገብቶኛል  "የእናቷ ፍቺ የችግር መነቀል ነው" መሆኑን ገልፃልኛለች ። በኔ ፍቺ ደግሞ ማን ሊሞት ነው የሚል ጥያቄ ህሊናዬን ወጥሮ እረፍት ነስቶኛል፣ እሷን ነው እህቷን ? አክስቷን ወይስ ማን? በሚለው የጥያቄ ናዳ ህልም ፣ የእውን አለም ስጋት ሆኖብኛል ምን ይሻለኛል? ለነገሩ ተውት "አበው ናቸው እመው? ህልም እንደፈቺው ነው! " ብለው የለ?! በእናቷ ፍቺ ያድርገው በሚለው ፀሎት እስክ እገዙኝ!!

ወገሬት!!