Sunday, March 19, 2017

" የ ም ሞ ተ ው  ዛ ሬ  ማ ታ … "


#ሳteናw

… አንተ አኔን ልትውሸደኝ? አለው ቡፌት በስራ የመጣ አለመግባባት ከተፈጠረበት ሌላኛውን የመሿለኪያ አባል ሙልጌን፣ ሊሸውደው ያደረገው ጥረት አማሮት…

… አታውቀኝማ ምን ታደርግ? መርካቶን ከፀጉር እስከ ጥፍሯ፣ ሸገርርን ከአፍ እስከ ቂጧ እንደ ማውቃት? ብሽቅ "ከች" ነትን (መጤነትህን) ረስተህ ለዚህም በቃህ? ጉድ ነው "ጋኖች አለቁና፣ ምንቸቶች ጋን ሆኑ" አሉ የሆንክ ጋን ነገር።

ሙልጌ እንደ ላውንቸር ያለ ማቋረጥ የሚንካካውን ሳቁን አጅቦ ለሌላ ሳቅ የሚጋብዝ ጥያቄውን ጣል አደረገ።
"ካካካካ የሸገር አፏ የት ነው? ቂጧስ?"

"እንደሱ ነዋ ሚባለው! አለማወቅህን አውቀህ፣ ለማወቅ መጠየቅህ በራሱ አዋቂነት ነው…
"ለቀማንድህን ትተህ አስኪ… ?" በመልሱ ለመሳቅ ጓግቶ … ሙልጌ

"አፏ ያው ልክ እንዳንተ አፍ ከጧት እስከማታ ጫት ስለማያጣው ጫት ተራ ነው። ቂጧ ደግሞ ቆሼ!።

በምልልሳቸው እንደ ጠረጴዛ ቴኒስ ጨዋታ ተመልካች አንገቱን ከቡፌት ወደ ሙልጌ፣ ከ ሙልጌ ወደ ቡፌት  ያመላልሱ የነበረው የመሿለኪያዋ ወጣቶች። በቡፌት መልስ ሳቃቸውን አፈነዱት… ካካካካከካካ…

   የመሿለኪያን ወጣት አባላት ለየት የሚያደርጋቸው ይህ ነው። ምን አለመግባባት በመካከላቸው ቢፈጠር ይተላለፋሉ። በቀልድ አጅበው መሳቂያ ያደርጋሉ እንጂ ለፀብ ብሎም ለቂም አይገባበዙም። ዛሬም በቡፌትና በሙልጌ መካከል የተፈጠረችው አለመግባባት በቀልድ ተዋዝታ ተደመደመች።

"አረ ባካችሁ ሳቅ ቀንሱ ሼም ነው! ቆሼ ተብሎ ሚታወቀው አካባቢ የቆሻሻው ክምር እንደ በረዶ ግግር ተንሸራቶ ላለቁ ሰዎች የሀዘን ቀን መታወጁን ዘነጋችሁት እንዴ? ቀዥቃዣው ሳተናው ነበር ከልቡ በሆነ ስሜት ጓደኞቹን የገሰፀው።

" በጣም ያሳዝናል? እኔ መጀመሪያውኑ እዛ አካባቢ መኖሪያ ቤት መገንባቱ እራሱ ገራሚ ነው። ለመሆኑ በመንግስት የተመራ፣ ለኑሮ ምቹነት በመሀንዲንስ ቦታው የተጠናና  ይሁንታ የተሰጠው ስፍራ ነው?  እኔ ይህን ለማመን ይቸግረኛል!" አለ አንዱ አባል።

"አዎ ልክ ነህ አደጋው የደረሰባቸው ቤቶች በመንግስት እውቅና ያላቸው ባይሆኑም በዛው አቅራቢያ ህጋዊ ቤቶች አሉ ሲባል የሰማው መሰለኝ፣ ቦታው እኮ እንኳን ለዚህ ዘመን ሰው፣ ከግዝፈታቸው የተነሳ ዛፍ ባአንድ እጃቸው ከስሩ መንግለው መንቀል ይችሉ ለነበሩት ለነቢዩ ሁድ ህዝቦች እራሱ አስጊ፣ ነው … ሳተናው ነበር።

"ከአደጋው ቡሃላ ከንቲባው ከስፋራው ተገኝተው የሀዘን ተካፋይ መሆናቸውና፣ በመግለጫቸውም አደጋው ለደረሰባቸው ቤተሰቦች ሀዘናቸውን መግለፃቸውን አልሰማህም?"

"ያሳዝናል!! ነዋሪውም ቢሆን በዛ ለጤና ጠንቅ  ለህይወት አስጊ እንደሆነ ባወቀው ስፈራ ላይ፣ "ናዳ መጣብህ ቢሉት፣ ተከናንቤያለው" እንዳለው ሞኝ ሰውዬ አይነት ነገር ቤት መገንባታቸው…"

"… በነሱ አይፈረድም በከተማዋ ያለው የመኖሪያ ቤት ችግር ነው፣ "መጀመሪያ መቀመጫዬን" በሚለው ብሂል ሄደው ነው በዚህ አደገኛ ቦታ ለመኖር ያስገደዳቸውና ህይወት ዋጋ ያስከፈላቸው።" አለሰያ ነጭ ሽንኩርት የዘወትር ልማዱን የኤር ፎን ገመድ ለመቀጠል እየቋጨ።

"ይሄ የከተማችንን የመኖሪያ ቤት ችግር ምን ያህል እንደሆነ የሚያሳይ ነው…

የከንቲባው ከቦታው መገኘት፣ ከዛ ቡሃላ ከተለያዩ አካላት ከአደጋው የተረፉትን መልሶ ለማቋቋም የተደረገው ርብርብ ይበል የሚያሰኝ ነው… ከንቲባው የተረፉትንና፣ እዛው አካባቢ ላሉ ነዋሪዎች፣ ቦታው ለመኖሪያነት የማይመችና፣ ለአደጋ የተጋለጠ በመሆኑ ሌላ ስፍራ እናዘዋውሯቿለን አሉ! አሉ።

ዘ ይግረም! ነው! እኔ እኮ የሚገርመኝ ይሄ ባህላችን እኮ ነው። አደጋ ከደረሰ ቡሃላ የምንረባረበው ነገር…  አለ በብስጭት …

"እንዴ ሌላው የራሱ ችግር ቋቅ ያለው ህዝብ የነሱን ችግር፣ ቀድሞ በምን ያውቃል?"

… ህዝቡን አላልኩም፣ አስተዳደሩን ነው። ነዋሪዎቹ ከአደጋው በፊት ስጋታቸውን ለሚመለከተው አካል አመልክተው ነበር! አሉ ግን ምላሽ አልነበረም።
በእውነቱ ከሆነ ነዋሪው ከማመልከቱ በፊት ቅድሚያ ሊገነዘቡ የተገባ ነበር። ግን ምን ታደርገዋለህ… ሁሌ እንደሞኝ ከስህተት እንጂ ከመጀሪያው ሊሆን ይችላል በሚል እንደ በሳል አዕምሮ  አይገመትም እኮ። … ትላንት የነዋሪው ስሞታ ላሽ ተብሎ፣ የሀዘን ቀን ማወጅ… ቀድሞው ነው እንጂ አልሞ መዶቀስ…አሉ።

አሁን በማን ሞት ከሚመለከተው አካል ውጪ ለዚህ አደጋ ሀላፍትናውን የሚወስደውስ ማን ነው?  አይ ሲስ ወይም ቦኮሀራም? እንዳልሆኑ መቼም ግልፅ ነው… ችግሩ ከሚመለከተው አካል ፈጣን ምላሽ   አለማግኘት ይመስለኛል። ግን እውነት እናውራ ካልን ጉዳዮቹ ቀድመው የሚደፍኑት ቀዳዳ አላቸው !"  አለ አንዱ

"ምንድነው ደግሞ?" አሉ ሁሉም የተመካከሩ ይመስል በአንድ ድምፅ፣ በተሰላቸ ሌላ መርዶ ለመስማት በተዘጋጀ መንፈስ።

"… የፑተለካው ጉዳይነዋ ። በዛ በኩል ፈጣን ናቸው። ከትራንስፎርሜሽኑ እቅድ በእጥፍ እጥፍ እጥፍ  ይቀድማሉ። እንቅፋት ነው ብለው ያገኙትን፣ ምን ያገኙትን የተጠራጠሩት ቀዳዳ በፈጥነት ይደፍኑታል፣ ያዳፉታል ወህኒ ወስደው በሩን ያዳፍኑበታል። አንቀፅ እየደረደሩ የክስ መዝገቡን በአንድ ሺህ ገፅ ይጠርዙለታል። በዶክመንተሪ ፊልም ጥላሸት የመቀባት ስም ማጥፋት ዘመቻ ያፋፍሙበታል። እድሜ እንደ ዳትሰን ሰፈር ደላሎች ጤፍ የሚቆላ ምላስ ላላቸው ልማታዊ ጋዜጠኞች፣ ሆሆሆ።  ከዚህ ውጪ ያሉ ጉዳዮች ቀድሞ ምላሽ የመሰጠት ዕድል የላቸውም። ብቻ ያሳዝናል በስንቱ ኡኡኡ እንደሚባል!   ምንጠይቀው የዛሬ ችግር፣ የእነ ጀለሴ የመልስ ለትናንት። ከህዝብ ጋር እኩል እየተራመዱ አይደለም!!  የትላንቱ አይደፈን ማለት አይደለም ይደፈን፣ ጎን ለጎን የዛሬውም ቢደፈን። እንደ ወጉማ ቢሆን መሪነት በራሱ ከህዝብ ፊት ሆኖ መምራት ነበር!! ጉዳዩ ግን ተገላቢጦሽ ሆኖ ተመሪው በብዙ እርምጃ ከፊት ዛሬ ላይ ቆሞ።፣ እንደ መጥምቁ ዮሃንስ በምድረ በዳ ሰሚ የሌለው ጩኸት ያሰማል። ዛሬ ሰሚ ቢኖር በስንት ጠዓሙ።

ባካቹ ተውት "የምሞተው ዛሬ ማታ፣ ገብስ የሚደርሰው ለፍልሰታ" አይነት ነገር ነው። የኛ ጉዳይ!!  እንደው እኩል ያራምደን ብሎ ከመፀለይ ውጪ ሌላ ምን ይባላል?"
"ምንም" ሲሉ በህብረት መለሱ።
ወገሬት!!!

No comments:

Post a Comment