Tuesday, March 28, 2017

"ተ ሰ ው  አ ለ ው  ብ ዬ … ተ ጅ ብ  ተ ዳ ብ ዬ "


#ሳteናw

  የዛሬው የመሿለኪያ ቆይታ በክርክር ተጀመረ። … በአዘቦት ቀን በተለመደው ስፍራ፣ ቦታና፣ ጊዜ ሁሉም ከየአቅጣጫው ወደ መሿለኪያዋ መቆያውን ይዞ ሲተም… መተዳደሪያቸው ሸቀጥ በመኪና ላይ መደርደር የሆነው ጃንደረባዉና ሙልጌ ደግሞ ቀን በስራ ሳቢያ ያጨቃጨቃቸውን ጭቅጭቅ ይዘው፣ ገና ከበሩ እየተጨቃጨቁ ተመሙ። ወጣቶቹ ቦታ ቦታቸውን ይዘው ቢቀመጡም፣ የሁለቱ አባላት ጭቅጭቅ ትኩረታቸውን ሳበው።
"ምንድነው ያጨቃጨቃችሁ?" ቡፌት ጠየቀ…
"ይኼ ነዋ!! እኔ ቢዝነስ ጠርሮብኝ፣ እሱ እንደ ጭላዳ ዝንጀሮ ከአንዱ መኪና ወደ አንዱ እየዘለል ሲሰራ ትንሽ ማይሰቀጥጠው፣ አንዱን ስራ ምናለ ቢለቅ እስኪ!!" ብስጭት እያለና፣ ለቅሶ በመሰለ ድምፅ ስሞታውን አቀረበ ግድ የለሹ መልጌ።
"እሺ ጃንደረባው ለምን አንዱን ስራ አልተውክለትም?" ሰያ ነጭ ሽንኩርት ጥያቄ አስከተለ…
" ልተውለት ብፈልግም፣ አልቻልኩም!!"
"ለምን አልቻልክም?"
" ሁለቱም ደንበኞቼ ካንተ ውጪ ማንም አይደረድርልም፣ ከፈለክ ዕቃ ሲመጣ በተራ በተራ ደርድርልን መኪናውን አጠገብ ለአጠገብ እናቆምልሃለን አሉኝ!! እኔ ምን ማድረግ እችላለው።"
"ቢሆንስ አንተ ብታሳምናቸው እንቢ አይሉም ነበር፣ ትንሽ ሰበብ ማግኘትህና መስገብገብህ እንጂ!!"  ብሎ ጣልቃ ገባ።

ጃንደረባው አንዳች ነገር ለመግዛት፣ ክርክሩን አቋርጦ "ቆይ አንዴ መጣው!" ብሎ ከመሿለኪያ ወጣ…

  ዝምተኛው ጄጃን፣ እንደሁሌው ዝም፣ ብሎ ሲያዳምጥ ቆይቶ፣ በንግግራቸው መሃል "መስገብገብህ እንጂ…"  የምትለዋን ሀረግ ይዞ በስግብግብት ዙሪያ የራሱን ግንዛቤ በማስታወሻው ላይ ማስፈር ጀመረ …

  ስግብግብነት መቼ ተጀመረ ለሚለው ጥያቄ እንደኔ እንደኔ መልሱ፣ ህይወት ያለው ነገር ምድር ላይ መኖር ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የሚል ይሆናል። የጅማሬውም ባለቤት የአዳም ልጅ ቃየል ነው። ለወንድሙ አቤል ሚስትነት ትገባው የነበረችውን የራሱን መንትያ ስሟ ማን እንደ ነበር እኔንጃ! ብቻ ለኔ ካልሆነለች በሚል ቀወጠው አሉ። እነ አዳም አረ መስሚያችን ጥጥ ነው፣ ላሽ በል ሲገጩት። መንትያ ወንድሙን በራስ ወዳድነት፣ በስግብግብነት ስሜት አቤልን በሳንጃ ይሁን በአጃራ አስጫረው። በቃ አዚህ ጋር ስግብግብነት "ሀ" ብሎ ቢጀመምርም "ፖ"  ብሎ የቋጨው አልተገኘም። ሁሌም ይቀጥላል። ህይወት እስካለች ዑደቷን እስካላቆመች ድረስ። ሰግብግብነት ራስን ብቻ የመውደድና ስለሌላው ምንም አለመጨነቅን ያመለክታል። በሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን በእንስሳዎችም ላይ ይስተዋላል… …  በእርግጥ እንስሳት ቢስገበገቡም ባይስገበገቡም አይገርምም። ምክኒያቱም እንደስው ክፉ ደጉን የሚለዩበት የሚያመዛዝኑበት አይምሮ ስላልተፈጠረላቸው። ሊግርመን የሚገባው  አሳቢ ተብየው የሰው መስገብገብ ነው። ሰግብግብነት የእድገት እንቅፋት፣ የሰላም ጠንቅ፣  የልማት ፀር ነው!!"  እንዲሉ  እነ እንትና።

…"ብስገበገብማ መች እሱ ይስራ ብዬ እጠይቃቸው ነበር፣ ችግር አለብህ የራስህን እንጂ የሰውን አትረዳም!!"   እያለ ጃንደረባው ወደ መሻለኪያዋ ተመልሶ ሲመጣ

ጄጃን ፅሁፉን ገታ አድርጎ ወደነ ጃንደረባው ክርክር ቀልቡን መለሰ…

"እሺ እንደረዳቴ አድርጌ ላሰራው ብለሃቸዋል?" ሳተናው በመስቀለኛ ጥያቄ …
"አላልኩም…"
"ለምን?"
"እኔንጃ በሰዓቱ ሀሳቡ ስላልመጣልኝ ይሆናል…

ይህን እየተባባሉ ጄጃን … ከቀናቶች በአንዱ በታክሲ ውስጥ አንድ በመጠጥ ስካር አቅሉን የሳተ ተሳፋሪ፣ የታክሲው ራዲዮ ስለብሄር ብሄረሰቦች ቀን፣ በውጪ ዜናው ስለ ፅንፈኛው ቡድን አይሲስ፣ ተናግሮ  ሲያበቃ ሰካራሙ ዜናዎቹን ተከትሎ የተናገረውን አስታወሰ…
"ምድረ ሴረኛ!!" ሲል ጀመረ ሰካራሙ ተሳፋሪ መጠጥ ባኮላተፈው አንደበቱ እየተንተፋተፈ…"ምድረ ሴረኛ … ማንን ለማታለል ነው? አይሲስ ቅብርጥሶ የሚሉት… አይሲስም በለው ኢቦላ፣ በአለማችን የሚከሰቱ  እልቂቶች ምንጫቸው እንደ ሎተሪ ተፍቆ ቢታይ በእርግጠኝነት የኋያላን ሀገራት ሴራ ሆኖ እንደሚገኝ አትጠራጠር …ህቅ!! አዎ! ለራሳቸው ምቾት ሲሉ በሴራቸው ለምቾታችን ስጋት ይሆናል ያሉትን ሀገርም ሆነ ግለሰብ ላይ አደጋ ከማድረስ ወደኋላ ያሉበት ጊዜ የለም። እንቅልፍ አጥተው ሌት ተቀን ምድር ቆፍረው ሰማይ ቧጠው አላማቸውን በማሳካት ላይ ናቸው፣ እንደኔና እንዳንተ አይነቱ በደሃና በመካከለኛ ደረጃ በሚገኙ  አገራት የምንኖር ምስኪኖች የነሱ የሴራቸው ሰለባ ነን፣ ህቅ!!…

ታክሲዋ፣የሰካራሙ ንግግር ነገሰባት።

  …በስልጣኔያቸው የበከሉት የአየርን ንብረት፣ ቀሪዋን እየተነፈሱ ይቀራመቱናል በሚል ይሁን በሌላ የሚስኪኑን እስትንፋስ ለመቁረጥ ወደ ኋላ ያሉበት ጊዜ እርሳው…፣ አይሲስም  የእርስ በእርስ ፍጅት፣ ምንጩን ለማግኘት እንደ ቱባክር ተርትረህ ጫፉ ስትደርስ እነሱን ታገኛለህ። የሚስኪኑ መስዋዕትነት በዚህ አይቋጭም። የራሳችን ዜጎች የምንላቸው መሪዎችም ለራሳቸው፣ ወይም ለፖለቲካ ድርጅታቸው ሲሉ እኛን ለመስዋዕትነት የቀረበ ሙክት ያድርጉናል። አይሄሄሄ ብዙ አታናግሩኝ እስኪ … ህቅ!!"(ማን ተናገር አለው እስኪ?)… ተሰው አለው ብዬ ተጅብ ተዳብዬ" ነው ነገሩ…ህቅ!! ህቅታው አይሎ!! ሊያስመልሰው ሲዳዳው፣ አጠገቡ የተቀመጠው ተሳፋሪ፣ ሻንፓይኑን አርከፈከፈብኝ በሚል ወደ መስታወቱ በሽሽት ተለጠፈ። (ሊዘል ነው እንዴ?) "ይገርምሃል!! … ለስጣናቸው እድሜ አዎንታዊ ያሉትን  አስተሳሰብ፣ ወደድክም ጠላህም አስረድቶ ከማሳመን ይልቅ በሃይል ይጭኑብሃል። አስተሳሰባችን እኛነታዊነት ያለው በምንፈልገው መልኩ ሳይሆን እነሱ እንደሚፈልጉት መልኩ እንዲሆን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስገድዱሃል። ይህም የመነጨው ከስልጣን ፍቅር የተነሳ ነው። ስግብግብነት በለው። ይበልጥ የሚገርመው ደግሞ!! ይህን ትውልድ ብቻ ሳይሆን መጪውን ትውልድእንኳ በሚፈልጉት በመልኩ ለመግዛት ያላቸው ፍላጎት… ዛሬ የሚሰሩት በመልካም ስም የሸፈኑት ሴራቸው ይናገራል። ለምሳሌ በብሄር ብሄረቦች ቀን ስም ህዝብን ለመለያየት፣ ሌላው ቀርቶ በሚዲያ የሚሰጠው ሰፊ የአየር ሰዓት ምን ያህል ስለ ልዩነት ሰበካ እየለፉ እየደከሙ እያለ የምናውቀው ሀቅ ነው… ህቅ!! ድርጊቱ ምነው ስለ አንድነት እንዲህ ትኩረት በተሰጠ ያስብላል። … እውነት ያንተ ባህላዊ አመጋገብ፣ ያንተ ባህላዊ ጭፈራ፣ ስቧቸው በመልካም መንገድ ወስደውት እንዳይመስልህ…ጉዳዩ ሌላ ነው። ህዝብን ለያይቶ ለመግዛት ካላቸው ፅኑ ፍላጎት እንጂ!! እውን የኢትዮጲያን ጉራማይሌ ውበት ሲተነትኑ እነደሰይመስልህ። የልዩነት እርከኑ ሰፍቶ የክፋት አረም እንዲያፈራ …ነው። አዎ ዛሬ ደግሞ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በሚል የበግ ለምድ እንደለበሰ ቀበሮ ላዩን ሸፍነውት ውስጡ መርዝ የሆነውን ሴራ የሚያርከፈክፉብህ…
የመጨረሻ የሚያሳፍረው ድርጊት  ደግም በዚህ ትውልድ ብቻ ሊቆሙ አለመቻላቸው… ህቅ!!  ገና ክፉ ደጉን ለይተው የማያውቁ ህፃናትን በየትምህርት ቤታቸው የትምህርት ገበታ ጊዜያቸውን፣ ለዚህ እኩይ አላማ ማባከናቸው። አንተ የሀደሬ ኮፍያ ለብሰህ ና፣ አንተ የአፋርን ሽርጥ አሸርጠህ አንደትመጣ እያሉ፣ ጨቅላ ህፃናቱን የተለያየን ነን የሚል እሳቤ ይዘው አድገው፣ ለነገ አገዛዛቸው…"

ሰካራሚ ድንገት ንግገሩን ገታ አድርጎ "ሾፌር!! … ምነው ከወትሮው መንገዱ ረዘመብኝሳ፣ መንገዱ ማታ ማታ  ይለጠጣል እንዴ…?"

የተሳፋሪው ሳቅ አጀበው። ካካካካ… ቂቂቂቂ

… ለዛ ይሆን ሲመሽ ታሪፍ የምትጨምሩብን? ካካካካ… ቂቂቂቂ

ሰካራሙ ወሬውን ሳይጨርስ ከመድረሻው አልፎ መሄዱን ሲረዳ…
"አረ አሳለፍከኝ!!  ወራጅ አለ!!" ብሎ እንደ አንደበቱ እየተንተፋተፈ ወረደ።

ጄጃን ከትውስታው ሲመለስ ጃንደረባውና ሙልጌ ተስማምተው፣ ሲሳሳቁ፣ አፍ ለአፍ ገጥመው ሲያወጉ ተመለከተ።

"ከምኔው ፍቅር በፍቅር ሆኑ?"

"አንተ ባገሩ የለህም!! ማለት ነው!! ቆይ ምንድነው ዝም ብለህ ምትቸከችከው፣ ምታሰላስለው? ያው ታቀው የለ!! በኛ ውስጥ ረዥም እድሜ ያለው ፀብ አለመኖሩን። ጃንዴ! ከሰራው ገንዘብ የተወሰነ ቦጨቀለታ።"
የመሻለኪያዊያንን የተካፍሎ መብላት ባህል ጠንቅቆ የሚያውቀው ጄጃን፣ በነገሩ ሳይገረም፣ በስንት ጊዜ አንዴ የሚያፈነጥቀውን ፈገግታ ብልጭ፣ አድርጎ ወደ ዝምተኛነቱ  ባህሪው ተመለሰ።

ወገሬት!!

No comments:

Post a Comment