Sunday, January 8, 2017

" የ ሀ ገ ር ፍ ቅ ር "

#ሳteናw

    ሁሉም ወጣት እንደተለመደው በመሿለኪያዋ ተሰብስቧል። ከሬዲዮኑ … የቴዲ አፍሮ ላምባዲና እየተስረቀረቀ የመሿለኪያን ድባብ ተቆጣጥሯል። አባላት በሞላየቴዲን ዜማ በሃሳብ ተውጦ ይሰማል። በተለይ … አንዱ!! በየስንኙ መሃል በአይነ ህሊናው ግጥሙን ከህይወቱ ጋር  የሚገናኘውን ነጥብ  ያምሰለስላል።

አይኖቼ አያዩ ብርሃን የላቸው፣
በልጅነቴ ድሮ አጥቻቸው።

… በልጅነቱ ያጣቸው አሳዳጊ አያቱ: አይኑ ላይ ድቅን አሉበት። አያቱ አይኖቹ ነበሩ።  እንዴት በፍቅር እንዳሳደጉት ርህራሄ እንክብክባያቸው አንድ በአንድ ታወሰው። እንዳይኑ ብሌን የሚያያቸው አያቱን ካጣ ቡሃላ ያሳለፈው ፍቅር አልባ ህይወት፣ ያጣቸው ነገሮች፣ በብቸኝነት ከሰው ሳይስማማ ያሳለፈው ፣ የመኖር ትርጉሙ ከህይወቱ  ውስጥ ሊያገኝበት ያልቻለበት ጊዤ፣ በአንድ በአንድ ድቅን… ሲልበት… ግድ የለሽ ህይወቱ በአንድ ሰው ሳቢያ መስተካከሉ። ከአያቱ ያጣው የፍቅር ክፍተት መሙላቱ የሚኖርለት የሚሞትለት ሰው ማግኘቱ፣ የመኖር ጉጉቱን እንደጨመረው። ለካ ሰው  ፍቅርን ካጣ ኖረ ሞተ ጉዳዩ አይደለም? የሰውን ልጅ ለመኖር ተስፋና ገጉት የሚፈጥርለት ፍቅርና ተስፋ ሆኗል። እያለ ሲያውጠነጥን።

… ሰያ ነጭ ሽንኩርት
"ሀገር ማለት ህዝብም ጭምር ነው።" ሲል ድንገት የተናገረው ቃል ከአሳቡ አባነነው።

"ማለት?" አንድ አባል ጠየቀ።

ሰያ ቀጠለ "ዛሬ እያንዳንዳችን  ለሀገራችን ያለን የፍቅር ወይም የግድየለሽ ስሜት ዝም ብሎ በድንገት የተፈጠረ አይደለም አንድ አመክኒዮ አለ።"

… ልክ ነህ በሚል ጭንቅላቱን  ነቀነቀ ሳተናው። በአንድ በኩል በውስጡ የሚያምሰለስለው ነገር በመነሳቱ በግጥምጥሞሹ እየተገረመ።

" እንዴት?" ሲል ሀሳቡን እንዲያብራራ  ቡፌት ሌላው አባል ጥያቄውን ሰነዘረ።

ሰያ ጎሮሮውን ጠረገና።
"…  ዛሬ ሃገራችን የመውደድ ወይም የመጥላት ስሜት ጀርባ፣ እያንዳንድሽ በህይወትሽ ላይ የተፈጠረ እውነታ አለ…
"ጀለሴ በትርፍ ሰዓትህ መፈላሰፍ ጀመርክ እንዴ? " ብሉ ሃሳቡን አቋረጠበት ጃንደረባው (ፂም አልባ ፊቱ ሁሌም ህፃን ያስመስለዋል)።

"ቆይ ዝም በል እስኪ!" አለው ቡፌት የሰያ ማብራሪያ እንዲቋረጥ ስላልፈለገ።
… ሰያ ጃንደረባው ያቋረጠበትን ሀሳብ ቀጠለ…

"… አዎ ለዛሬው ለሀገር ፍቅር ያለን ስሜት ከየትም የመነጨ አይደለም። ከህይወታችን እንጂ። እንደውም በራሴ ህይወት ምሳሌ ልስጣችሁ … እኔ ለሃገር ፍቅር በልቤ ውስጥ ያለው ቦታ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ምንም ነበር ማለት ይቻላል።

"እንዴት?"

"እንዴት ማለት ጥሩ! ይህ ለሃገሬ የሞተ ስሜት ለምን ሊፈጠር እንደቻለ የአስተዳደግ ሁኔታዬ ይመልሰዋል።

… እናቴ እኔን ስትወልድ ነበር የሞተችው። በማህበረሰቤ ዘንድ እናቱን ያጣ አሳዛኝ ሚስኪን ሳይሆን ገደቢስ፣ ገፊ እባል ነበር። ከዚህ ማህበረሰቤ ያተረፍኩት እናቱን እንዳጣ ህፃን እዝነት፣እንክብካቤን  ፍቅርን ሳይሆን ጥላቻን ሆነ። ታዲያ ፍቅር ላልሰጠኝ ማህበረሰብ ከየት አምጥቼ ነው ፍቅር ልሰጠው የምችለው።ቤታችን የሚቀጠሩ ሴቶች፣ ልብሴ ላይ አምልጦኝ ሽንቴን በሸናው ቁጥር እየቆነጠጡኝ እየደበደቡኝ አድጌ፣ እንዴት ነው ለሴት ልጅ ክብርና ፍቅር የሚኖረኝ። በሙያው ለማህበረሰቡ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለው ወላጅ አባቴ ፣ለኔ ቁብ ሰጥቶት አላሳደገኝም። ሌላው ይቅር አቅፎ ስሞኝ አያውቅም። ፍቅር ሰጥቶ ላላሳደገ አባት ፍቅር መስጠት መቻል ዘበት ነው… አያችሁ ለዚህ ነው። ለሃገራችን ያለን የፍቅር ስሜት ያለምክኒያት አይፈጠርም ያልኩት።

"ታዲያ የግለሰቦች ጥላቻ እንዴ ሀገርን ለመጥላት መንስኤ ይሆናል?"

በጣም ጥሩ!! አለ ሰያ…  ሀገር ማለት ህዝብ ነው ብለናል። ያለ ህዝብ ሜዳው ጋራው፣ ሸንተሩሩ ወንዙ፣ ቁልቁለት ዳገቱ ደን እንጂ ሌላ አይደለም። ስለዚህ ሀገር ማለት ህዝብም ጭምር ነው። ህዝብ ደግሞ የግለሰብ፣ የቤተሰብ፣ የማህበረሰብ ስብጥር ነው። አለቀ፣ ከቤተሰብ ከማህበረሰብህ ጥላቻን ከተቀበልክ፣ ምላሽህ ጥላቻ ነው። ሀገርን ለመጥላት ከዚህ የበለጠ ምክኒያት ያስፈልጋል?" ሲል ወደ ሁሉም ተገላመጠ። በስሜት ያወራ ስለነበር መርፌ ቢወድቅ እንኳ በሚሰማ ሁኔታ ነበር በመሻለኪያ ፀጥታ የሰፈነው። ከሰመጠበት የስሜት ንግግር፣ ወጥቶ የፈገግታ ብልጭታ እያሳየ ቀጠለ…

"…  በህይወት ዑደት ካልጠበከው አካል የምታገኘው ፍቅር፣ ለሃገር ፍቅር እንዲኖር ያደርጋል። ለኔም ይህቺ መሿለኪያ ውስጥ ከእናንተ ዘር፣ ጎሳ፣ ብሄር፣ እምነት የማይለየው ፍቅር ፣ ለሃገሬ ፍቅር እንዲያድርብኝ አድርጎኛል። በህይወት ለመኖር ብሎም ለሃገሬ አንድ ነገር ለመስራት ከፍተኛ ጉጉት ፈጥሮብኛል። አየህ ለሃገርህ ፍቅር እንዲኖርህ ከቤተሰብ፣ ከማህበረሰብ ልዩነት አልባ ፍቅር መተሳሰብና መዋደድ መሰረት ይሆናል። ዛሬ የወጣቱን የሀገር ፍቅር ስሜት፣ ለመመለስ ለሀገር ለወገኑ በዘርፉ አንዳች ነገር እንዲፈጥር ጉጉት እንዲያድርበት፣ ፍቅር ማስተማር ያስፈልጋል።

ሰያ ይህን ከህይወቱ ጋር የተቆራኘውን እውነታ ሲተነትን። የመሿለኪያ የወጣት ስብስብ አባላት ደስታቸው ወሰን አጣ። የባለታሪኩን አባል ለሃገር ያለው አመለካከት አቅጣጫውን በፍቅር ለመቀየር ሰበብ መሆናቸው ስብስባቸውን ለማዝለቅ አስተሳሰባቸውንም ከመሿለኪያ ውጪ ለማስፋት ምኞት አደረባቸው። ሁሉም እየተነሱ ሰያን በስሜት አቀፉት።…

ወገሬት!

No comments:

Post a Comment