Tuesday, July 12, 2016

"የማዕረጎች ሁሉ ማዕረግ"

"የማዕረጎች ሁሉ ማዕረግ"
#ሳteናw

…  አንድ ጉርሻ ጠቅልዬ ስጎርስ … አታምንም…(ትን ብሎኝ ፣ ፍንግል፣ድፍት የምል ይመስላታል… ካሁን አሁን… አንቆት ውሃ ሊጠይቀኝ ይችላል በሚል… … ልትጎርስ…  የጠቀለለችውን ጉርሻ… አየር  ላይ እንዳንጠለጠለች… ጉርሻዬ በጎሮሮዬ ተንሸራቶ እስኪወርድ… በተጠንቀቅ… ትከታተላለኛለች… መዋጤን ስታረጋግጥ… አየር ላይ ያስቀረቻትን ጉርሻ… (ትጎርሳታለች) !!የምልህ መስሎህ ከሆነ ተሳስተሃል!! … አትጎርሳትም…
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

   በእንግሊዝ ትልቅ ስኬት ከሚሰኘው ሰርነት(ser) ማዕረግ ይበልጣል። ማርስ ላይ ስም ከሚያስፅፈው ሎሬትነት ይልቃል። አለማዊ ዕውቀት ከሚያስጎናፅፈው ፕሮፌሰርነት ይበዛል።  ከማዕረጎች ሁሉ ይጠጥራል። ይህ ፆታ ለይ ማዕረግ ለራስ በራስ በሆነ ጥረት እንደ ሚገኙት ኘሮፌሰርነት፣ዶክተርነት፣ ወይም ሎሬትነት ማዕረጎች ከትልልቅ ትምህርት ተቋም… አልያም መሰል ድርጅቶች አይገኝም።

…  ያለምንም፣ የቀለም እውቀትና የሀብት ስኬት ለወላድ ሔዋንያን ተፈጥሮ የምትቸረው ማዕረግ ነው !እናትነትን! ለራሷ ሳይሆን ለአብራኳ ክፋይ የራሷን ህይወት፣ ደስታ፣ምቾት፣ጥጋብ፣ አሳልፋ በመስጠቷ  የምትጎናፀፈው ማዕረግ ነው!! እናትነት…!!የማዕረጎች ሁሉ ማዕረግ።

  እናት ለልጇ መኖር፣ በልጇ የእውነት ደስታ ሚሰማት፣ ስትወልደው አይደለም። ዶክተር የሁለት ወር ቅሪት ነሽ (ዘመናዊ እናት ከሆነች)ካላት፣ ወይም ነብሰ ጡር መሆኗን ካወቀችበት፣ ቅጽበት ይጀምራል።
ከዛስ… ሆዷ ውስጥ ያለው ፅንስ ተንፈራግጦ ሲረግጣት  በደስታ ትፈድቃለች። እስክትወልደው ድረስ እርግዝናዋን ትጠነቀቅለታለች። ህመሟን ውጣ ምቾቱን ትጠብቃለች።
መውለጃዋ ሲደርስ ልቧ ከበፊቱ እጥፍ የደስታ ድቤዋን ትደቃለች። በወሊድ ወቅት፣ ያስጮሃት፣ ያስጨነቃት፣ ምጥ ስትገላገል… ይህን…  ረስታ ከነደሙ በፈገግታ ከአዋላጅ እጅ ትቀበላለች። ስታጠባው…ወተት የሞላው ግቷ…  አፍኖ ይገለው ይሆን?… በሚል ስጋት የምታደርገው ጥንቃቄ ቦምብ አምካኝን ታስንቃለች። የራሷ ጉንጭ ደርቆ፣ ስለልጇ ድንቡሽቡሽነት ትተክዛለች። ህፃኑ ድክ ድክ እያለ ሲንቸፋቸፍ… ካሁን አሁን ወደቀ! ምን ነካው? ስትል ቀልቧን…ትስታለች። ነጋ ጠባ ከአፉ እየተንዠረገገ የሚወርደውን ለሀጭ በአፏ ትቀበለዋለች፣ መጠየፍ አይነካካትም፣…  ይህ ለልጇ የምከፍለው መስዋዕትነት… ሁለቱም እስካሉ ድረስ ይቀጥላል…  እናትነት… በምንም ብህር እስከ ፅንፍ አይገለጥም… በምንም ውለታ አይመለስም፣ … ።

ስለ እናት ማንሳቴ ከእናቴ ጋር ያደረግነው፣  የሁሌና የማታውን ሁኔታ …ለርዕሴ ማጠናከሪያነት እንዳክለው ገፋፋኝ…

… ክፍት ሆኖ የሚጠብቀኝን…  የግቢውን በር አልፌ … ገብቼ፣ ከውስጥ ቀርቅሬ። … የዋና ቤቱን በር ከፍቼ ስገባ ነው… ፍራሼ ላይ ጥቅልል ብላ ብርድልብሴን ለብሳው… ትኩረቷ እኔን በመጠበቅ… አይኗ በሩ ላይ እንደተተከለ… አይኔና አይኗ ሲጋጭ… ማውቀው!! ከሰላምታና፣ ከስራ ሁኔታ ጥየቃ ቡሃላ… ልብሴን ቀይሬና… አጠገቧ… ተቀምጬ ሞባይሌን መነካካት ስጀምር… እራት ለማቅረብ ጉድ ጉድ ማለቷን ትጀምራለች።
የራሴን ምቾት የጠበቁ ጥያቄዎች አነሳለው…!!
"ውሃ መጣ እንዴ ዳዳ ?"
"አዎ"… ስራዋን እያከናወነች።
"ልብሶቼስ ታጠቡ…?"
"አዎ"።
ዝምታ ሲነግስ ቤቱ ጭር ሲልብኝ…
"ይሄ ቲቪና ሪሲቨር በቃ ተቃጥሎ ቀረ?"
"ማን ያሰራው ታዲያ…?" … ሀላፍትናው አንተን ነው የሚመለከተው በሚመስል ሁኔታ።(ግን ደፍራ አሰራው አትልም፣አስጨንቀዋለው በሚል)
"እንዴ! አሰራዋለው አላለችም እንዴ?"
"ማን?"… ስራዋን አቁማ እያየችኝ።
"ሶፊ ነቻ!!"(እህቴን)
"ምፅ!!የኔ እናት ስራው አልተመቻትም መሰለኝ… ለዛ ነው?!"ስራዋን ካቆመችበት ትቀጥላለች።
"የራሷ ጉዳይ!! ብዬ ተወዋለው ድሮም ስለማንስማማ ትንሽ ነገር ነው /ልገላምጣት፣ልታመናጭቀኝ/የሚበቃን። ሁለታችንም ሀይለኞች ነን። ትንሽ መጨቃጨቅ ስንጀምር፣ የጭንቀት፣ ፈገግታ ታሳየናለች። ለሁለታችንም የማያዳላ ሽምግልና ትቆማለች።

እናቴ እራቱ አቀረበች።

… አብረን ስንበላ… አንድ ጉርሻ ስጎርስ … አታምንም…ትን፣ ፍንግል፣ድፍት የምል ይመስላታል… ካሁን አሁን አንቆት ውሃ ሊጠይቀኝ ይችላል በሚል…ልትጎርስ…  የጠቀለለችውን ጉርሻ… አየር  ላይ እንዳንጠለጠለች… ጉርሻዬ በጎሮሮዬ ተንሸራቶ እስኪወርድ… በተጠንቀቅ… ትከታተላለኛለች…(ብዩ እንጂ)   መዋጤን ስታረጋግጥ… አየር ላይ ያስቀረቻትን ጉርሻ… (ትጎርሳታለች) !!የምልህ መስሎህ ከሆነ ተሳስተሃል… ካላጎረስኩህ ትለኛለች… አልሰማትም… አንቺ አልበላሽም ጉረሺው ብዬ በግድ እንድትጎርስ አደርጋታለው… ብዪ…  ብላ!  በሚል ስንጨቃጨቅ… እሷ በቅጡ ሳትበላ እኔ እጠግባለው!!

  በቃኝ ብዬ ስነሳ የሚገጥመኝን ንትርክ አስባለው…!!  ከመነሳቴ በፊት… በአይኔ በቅቶኛል በሚል እለማመጣታለው… "ጀመረህ ደግሞ!" ብላ እንደመገላመጥ ታየኛለች… ቀልቧን ማስከፋት ስለማልፈልግ…  ልምምጤን በአንደበቴ ጀምራለው…!!

"ወላሂ ዳዳ በጣም ነው የጠገብኩት… እየው ካላመንሽ ሆዴን እዪውማ?" ብዬ ቲሸርቴን ገልጬ ሆዴን ነፍቼ አሳያታለው…! 
"አቤት?!ተበርቼ ሰላም…!!  ብላ ትስቃለች…ካካካካ… ። ሳቋን እንደ ሽፋን ተጠቅሜ… ላጥ ብዬ አጄን ልታጠብ  እነሳለው…  ማስታጠቢያው ጋር ሳልደርስ
"እሺ ይሄን ምን ላድርገው…!? " ስትለኝ…  እቆማለው። ድጋሚ ዞሬ… የማለቅስ በሚመስል ድምፅ…!!
"በናትሽ! የአንድ ጉርሻ  ቦታ የለም!!" እላታለው…
የውሸት በሆነ ኩርፊያ ወደ ማዕዱ ትዞራለች። እናትነት ይህ ነው። ምንም ብትበላ የምጠግብ አይመስላትም፣ ጠራርገህ ስትበላ… ካልጨመርኩ… ሌላ ግብግብ… አንድ ስኒ ቡና ከጠጣህ… ካልደገምኩልህ!።

በቃ ሁሌም ብቻዋን አይበላላትም… እንደተነሳው… በቃኝ® ትልና  ታነሳዋለች።

እኔ ሳሎን ቤት ስተኛ አስር አይነት ልብስ ሳትደራርብልኝና… "አረ በቃ አፍነሽ ልትገዪኝ ነው እንዴ?" ብዬ ካላስቆምኳት በስተቀር ብርድ ይነካሃል በሚል ስጋት መደራረብ አታቆምም!! 
እሷ መኝታ ቤት አልጋዋ ላይ ብትተኛም… ልቧ ከኔ ጋር ነው…የኔ ልብ ኢንተርኔት ላይ ተጥዳል…
"አንተ ልጅ በረደህ?" ከመኝታ ክፍሏ ድምፇ ሳስቶ ይመጣል።
"አይይይ" እላታለው… ትኩረቴን ከሞባይሌ ስክሪኔ ላይ ሳልነቅል… ትቆይና… በተመሰጥኩበት…
"ለሽንት ከተነሳህ ልብስ መደረብህን እንዳትረሳ?"…ዝም እላታው… ትኩረቴን በሳበው… ኢንተርኔት… ተውጬ…!
ድሜፄ ሲጠፋባት…!! ሰማከኝ!ሰሉ… ተኛህ እንዴ…??
"አዎ! ዳዳ…፣ ተኚ በቃ!!" እላትና!! ወደ ትኩረት ሰራቂዬ እመለሳለው… አንድ ሶስት ደቂቃ ዝም ካለች ቡሃላ አያስችላትም…
"ወይ ካልሆነ አልጋ ላይ ትተኛለህ…እንዴ?" ይሄኔ… ነቅላለው…
"ጥ!! አረ በአላህ ዳዳ! ምንም አልሆንም በቃ!" በነጭናጫና በጎላ ድምፅ ብዬ ጥያቄዋን ስጋቷን፣ እንድታቆም፣ ፈልጋለው። እንቅልፍ እስኪወስደኝ… ምቾቴን ለመጠበቅ በምታነሳው የጥያቄ ጋጋታ ማስተናገድ ግድ ይለኛል… ስለራሷ ደህንነት ተጨንቃ አትጠይቀኝም! ወይም እንድቸገር አትፈልግም!! ሁሌም ለራሴው!! ሁሌም ለወንድም እህቶቼ ነው ጭንቀቷ። ምን ታድርግ ተፈጥሮ ያደላት ማዕረጓ፣ነው!!  እናትነቷ!!
ረጅም እድሜና፣ጤና፣ጀነት ለማዙካዎቻችን!
ወገሬት!!
 

No comments:

Post a Comment