Wednesday, July 13, 2016

"ቀ ለ ማ ተ … አ ዳ ም"

" ቀለማተ አዳም  "
#ሳteናw

   አንዳንዴ ሳስበው ያለው የእውቀት መጠን በ30 ሚሊዮን መፅሀፍት፣ በአንደኝነት የሚመራው የኮንግረስ ላይብሪ ወይም በ22 ሚሊዮን መፅሀፍት የሚከተለው የቻይናው ላይብረሪ…  ይመስለኛል…
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

     ከፈለገ የአይምሮ ዶክተር፣ ከፈለገ ፖለቲከኛ፣ ከፈለገ ታሪክ አዋቂ፣ከፈለገ ሰዓሊ፣ ከፈለገ አንጥረኛ፣ ከፈለገ ፈላስፋ … የፈለገውን እየሆነ መፃፍ እንዲችል… አስችሎታል። አንዳንዴ ሳስበው በ 30 ሚሊዮን መፅሀፍት፣ በአንደኝነት የሚመራው የኮንግረስ ላይብሪ ወይም በ22 ሚሊዮን መፅሀፍት የሚከተለው የቻይናው ላይብሪ…  ይመስለኛል… ያለው ጥልቅ እውቀት…

በ1950 በአዲስ አበባ ተወልዶ … በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጂኦግራፊ የመጀመሪያ ዲግሪውን… ማስተርሱን በውጪ ባለ የትምህርት ተቋም አግኝቷል። ደራሲ አዳም ረታ።

  አዳም ረታ፣ የራሱ በሆነ የአፃፃፍ ስልቱ ይታወቃል። የፅሁፍ ስልቱ አወራረድ እስክትግባባው እያወዛገበ ቢያደክምህም… ከተግባባከው ቡሃላ እንዴ እያሳቀ፣ እያስገረመህ፣ እያመራመረህ፣… በመሀል ራሱን እያደነቅከው በሚቀያየር ስሜት ከድረሰቶቹ ጋር ትንሳፈፋለህ። ድንቅ በሆነ የአተራረክ ስልቱ… ልብ የማትላቸው ሁኔታዎችን በሚያስደምም አገላለፅ እየፈለፈለና እየለቀመ ከራሱ ጥልቅ አመለካከት ጋር አሟሽቶ፣አዋዝቶ በመተረክ  ለስነ ፅሁፍ የተፈጠረ መሆኑን አስመስክሯል።

የቃላት ሀብቱን መጠን በመፅሀፎቹ ደልዳላነትና አዲስ በሚሆኑ …  ቃላት ብዛት ያስመሰከረው አዳም ረታ ከአንባቢ ጋር የተዋወቀባቸው ቀደምት ስራዎቹ :-በጋዜጦች ላይ ከሚሳተፍባቸው ግጥሞችና ፅሁፎች ሌላ  "አባ ደፋርና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች" 1977። "ጭጋግና ጠል" 1980" (ከሌሎች ደራሲዎች ጋር የታተሙለት ስለነበር እንደ ወጥ ጥራዝ አብዛኛዎቻችን አናውቀውም) ማህሌት/1981/፣ ግራጫ ቃጭሎች/1997/፣አለንጋና ምስር፣እቴሜቴ ሎሚ ሽታ፣ ከሰማይ የወረደ ፍርፍር(2004)፣ ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ(2004)፣ ህማማትና በገና(2005)፣ እና መረቅ /2007/ናቸው። አልዋሽህም ሁሉንም ስራዎች ባላነባቸውም ግማሽ ያህሉን አንብቤያቸዋለው፣(እድሜ ለጀለሱካዬ ሱሌ)

(…ዳኛቸው ወርቁ በ“አደፍርስ” የኢፒሶዲክ ሕግጋትን አጋምሶ ለማስተዋወቅ ከሞከረ ወዲህ በአማርኛ ሥነ-ጽሑፍ በኢፒሶዲክ ተሟልቶ የተገኘ ድርሰት “ግራጫ ቃጭሎች” ነው። ይህቺ የአለማየው ገላጋይ ገለፃ ነች)።

በተለይ የግራጫ ቃጭሉን ገፀ ባህሪይ ዝምተኛው፣ ብቸኛው፣ ፈላስፋው፣  ከጎልሏቷ የሚቀመጠው መዝገቡን እንዴት ስተዋለው? የመረቁ አልአዛርም አይጠፋኝም…

   አዳም፣ በዚሁ፣አመትና ባሳለፍነው ወር ለአንባቢዎቹ… በቅርፅና ይዘቱ፣ የተለየ በገፅ ብዛቱ በኢትዮጲያ የረጅም… ልብወለድ ታሪክ፣ ክብረ ወሰን የነቀነቀቀ አዲስ መፅሀፍ ጀባ ብሏል። የስንብት ቀለማት በሚል ርዕስ ለንባብ የበቃው ይሔው አዲስ መፅሀፍ በንፋስ ስልክ ዙሪያ ያሉ ማህበረሰቦች… ውስጥ የመረጣቸውን ገፀ ባህሪያት… ሁሉንም ወክሎ… የመጡበትን የታሪክ ዳራ እየመዘዘ… ከነ ተለያየ አመለካከታቸው ጋር፣ በውብና ጥልቅ የስነ ፅሁፍ ችሎታው በራሳቸው አፍ ይተርከዋል። የስንብት ቀለማት በ960።ገፆች ፣ በ46 ንዑስ ምዕራፎች፣ በ8 አቢይ ምዕራፎች፣ በ350 ብር፣ ለገበያ በቅቷል።ምርጥ መፅሀፍ ነው አንብበው ግብዣዬ ነው…

የታመቀ የስነፅሁፍ ዛር የሰፈረብህ ከሆን ደግሞ…የአዳምን መፅሀፎች በደንብ እንድታነብ እመክርሃለው… ምክሬን ስትተገብር… የታመቀ  ዛርህን እንደ ድኝና ቀበርቾ ጢስ ዛርህ አስነስቶ… እንድትፅፍ እንድትቸከችክ… ስታዲያም ካጨናነቀ ደጋፊ ባልተናነሰ… ሞራል… ይሰጥሃል፣ አዳፍነህ ካፈንከው የስነፅሁፍ ተሰጦ ያነቃቃሃል… ቸክችክ ቸክችክ ይልሃል።
ወገሬት!!

No comments:

Post a Comment