Saturday, July 9, 2016

"ስምና … አመል "

"ስምና… አመል"
#ሳteናw

…  ዘንድሮ ግን ትውልዱ ስንቁ አንሶ አመሉ በዝቷል። ምን ያድርግ? ስንቁ ያነሰው አንደዛ ዘመን በግ በአምስት ብር ገዝቶ ቆዳውን በሶስት ብር እንዳይሸጥ ያደረገው ዘመን አመጣሹ የኑሮ ውድነት ነው። አመሉን ያበዛው ብሶት ሆነ። ሳይወድ በግዱ በጉያው የሚይዘው ስንቅ ጫት፣ በአህያ የሚጭነው ሸክም አመሉ፣ ሆነበት።

ታዲያ አፄ ሚኒሊክ በኛ ትውልድ ቢገኙ ኖሮ መልዕክታቸው … "አመልህን በአህያ፣በርጫህን በጉያህ"… አይሆንም ነበር ትላላችሁ?…
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

    ከቤተሰባችንና ከማህበረሰባችን ከወረስናቸው ብዙ ነገሮች ውስጥ፣ ሁለቱ ስምና አመል ናቸው። ስም :-መልክን፣ እምነትን፣ ምኞትን፣ ነባራዊ ሁኔታን … መሰረት ተደርጎ ቤተሰብ ያወጣልናል። ለልጁ ምንም ሀብት ማውረስ እንደማይችል የተረዳ ደሃ ቤተሰብ፣ ለልጁ ሀብታሙ፣ ሚሊዮን፣ ወዘተ የሚል  የሀብት ምኞት አዘል ስም ሲያወርስ ፣ የሀብታም ልጅ ከቤተሰቡ ስምም ሀብት ይወርሳል።

  በአንፃሩ አመል በአስተዳደግ ፣ በስነ ልቦናዊ ጫና ፣ባመዘንበት ፍላጎታችን በመሳሰሉት አብሮን ያድጋል። በዚህም የመጣ አመል መለያ ይሆናል። ልክ እንደ ስም። "ሌባው" ይባላል የእጅ አመል ያለበት ሰው።" አልያም አንባቢው የሚል መለያ ይሰጠዋል። ጠጪው፣ አጫሹ፣ቃሚው፣በ*ው፣ ታታሪው፣ ምላሰኛው፣ ቋጣሪው፣ ለጋሹ ወዘተ እየተባለ ፣አመልህን ያማከለ መለያ ስም ከማህረሰብህ ይሰጥሃል። ስምን ለራሱ ያወጣ እንደሌለ ሁሉ፣ አመልም ከማህበረሰብ ይወጣል።

  አንዳንዴ ቤተሰብ በተምኔት ያወረሰን ስምና፣ ከማህበረሰብ  የምንወርሰው ባህሪይ አይገጥሙም። በምሳሌ እንይ…

ሰውየው በጣም ታዋቂ ሌባ ነው አሉ። የሚኖርበት  አካባቢም በሌቦች ብዛት ይታማል። ይህ ሌባ ወንድ ልጅ ሲወልድ… የራሱ አይነት ሌባ እንዳይሆንና መልካም ልጅ እንዲሆንለት በመመኘት ስሙን መልካሙ ሲል ሰየመው። መልካም እንዲሆን የተመኘው ሌባ አባት እለት ከለት ዘርፎ የሚያመጣውን ነገር ህፃኑ መልካሙ እያየ አባቱን የማህበረሰቡን የስርቆት እንቅስቃሴ እያስተዋለ ያድጋል። ።ይህን እያየ ያደገው ህፃኑ መልካሙ፣ አባቱ መልካም  ወደ ሌብነት ለመግባት የማንምም ምክር ሳይሻ ከአባቱ የባሰ ሌባ ሆኖ ተገኘ። ይህን የተመለከተው አባት ለልጁ የሰጠው ስያሜ ወዲያው ቀየረው። ይባስ ብሎ እንደ አዲስ ሰየመው አሉ። ምን ያድርግ!! ስያሜውና አመሉ አልገጥም ቢለው ነው።

  እኔ በአያቴ የወጣልኝ ስም peace ነው (ወደ አማርኛ ከርብተው)። አያቴ ይህን ስያሜ ያወጣችልኝ እኔም በወቅቱ ሰላም ያልነበረበችው ሀገራችን ሰላማዊ እንድትሆንላት በመመኘቷ ነበረ። ምኞቷ በሀገሪቷ ሰላምነት ሲሰምር፣ በእኔ አዛ ባህሪ መከነ። ከስሜ ተቃራኒ ሆኜ ተገኘው። ይህን የታዘበች አንድ የመንደሬ ሴት፣ አንድ ለት በአንዳች ነገር ብጦልባት፣

"አንተን ሰላም ብሎ ስም ያወጣልህ ሰላም አይቶ የማያውቅ ነው!!" ብላ ከትውስታ ማይፋቅ ምሬቷን ጣለችብኝ።

"አዎ ስሜ ሲወጣ በሀገሪቱ ሰላም አልታየም" ልላት አልኩና ተውኩት… 

እኔና ይባስ ብቻ አይደለንም። የስያሜ ምኞቱ ሳይሰምር፣ በድህነቱ የዘለቀ ሀብታሙ፣ ደሀ ሆኖ ቀርቷል። አልያም ጤንንት የተመኙሉት ጤናው… በሽተኛ ሆኖ የሚቀርበት አጋጣሚ በበሽ አለ… አስበው ስሙ ቸሩ ተብሎ፣ እልም ያለ ቋጣሪ፣ገብጋባ፣ መንጠቆ፣ ጌታሁን ተብሎ የሀብታም ዘበኛ፣ ሰላም ተብሎ አገር ያቃጠለ አዛ ሆኖ ሲገኝ። ማሙሽ ተብሎ ተሰይሞ እድሜ ሰጥቶት ሲያረጅ ጋሽ ማሙሽ ብለህ ስትጠራው!! " ስምን መልዓክ ያወጣዋል እዚህ ጋር… አይነፋም። እንደ ስም አመልም ከቤተሰብና ከማህበረሰብ ተጀብቶናል። ልክ እንደኔ ና እንደ ህፃኑ ይባስ።

ሀገር በቀል የሆነ አባባል አለ፣

ግመል ምን ጭነሃል? ሽመል፣ ምን ያወዛውዝሃል? አመል!!።
እርግጥ ነው ግመል ያወዛወዘው ሸክሙ ከብዶት፣ ሳይሆን ልማድ አመሉ ነው።

የሰው ልጅ እንደ ስም ፣መልክና አሻራው ከሚለያይባቸው ነገሮች ሌላው አመሉ ነው።

አንድ ሰው የተለያዩ አመሎችን ቢያንፀባርቅም ከሁሉም የሚያመዝንበት አንድ አመል አለው። አመል ሁለት አይነት ነው። መልካምና መጥፎ በለው። ከሁለቱም ወገን ያልሆነ ሊኖርም ይችላል።

አመል ስል ይሄም ትዝ አለኝ

… አፄ ምኒሊክ በፋሺሽት ኢጣሊያ ሲወረሩ ክተት ባወጁ ጊዜ፣ ለዘማቹ አፅንኦት ሰጥተው ያስተላለፉትን መልዕክት ተከታዩ ነበር…

"አመልህን፣በጉያህ፣ ስንቅህን፣በአህያ"።

  ዘንድሮ ግን ትውልዱ ስንቁ አንሶ አመሉ በዝቷል። ምን ያድርግ? ስንቁ ያነሰው አንደዛ ዘመን በግ በአምስት ብር ገዝቶ ቆዳውን በሶስት ብር እንዳይሸጥ ያደረገው ዘመን አመጣሹ የኑሮ ውድነት ነው። አመሉን ያበዛው ብሶት ሆነ። ሳይወድ በግዱ በጉያው የሚይዘው ስንቅ ጫት፣ በአህያ የሚጭነው ሸክም አመሉ፣ ሆነበት።

ታዲያ አፄ ሚኒሊክ በኛ ትውልድ ቢገኙ ኖሮ መልዕክታቸው … "አመልህን በአህያ፣በርጫህን በጉያህ"… አይሆንም ነበር ትላላችሁ?…

ስለሰውና ባህሪው ብዙማለት ይቻላል … ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራልና ይብራ…

ስምን ለራሱ ያወጣ እንደሌለ ሁሉ፣ አመልም ከማህበረሰብ ይወረሳል። ልክ እንደ ህፃኑ ይባስ። ይህን ውርሳችንን መልካም ከሆነ መልካም፣ መልካም ካልሆነ ልንተራረም እንጂ ልንቃረንበት፣ በጅምላ ልንሰዳደብበት አይገባም። በተለይ በብሄርና፣ በሀይማኖት።

  እስካሁን… የተንዛዛውብህ፣ እንደ ፈላስፋ ያወዛገብኩህ፣ ለሌላ አይደለም…! እንደ ስምና መልካችን የተለያየውን አመላችንን፣ አስማምቶ  ያቻችለን፣ አጣጥሞ ያፋቅረን አንድነት ይስጠን ለማለት!!
ወገሬት!!

No comments:

Post a Comment