Wednesday, June 29, 2016

"የ ቄ ሳ ር … እ ን ባ"

  ወይኔ መንጌ መጨረሻዬ ይህ ሆነ? ለደቂቃዎች በዝምታ ተዋጡ። እንጥላቸው ዱብ… ሀሞታቸው ፍስስ… ቅልጥማቸው ድቅቅ… ወገባቸው ዛለ… ጉልበት ከድቷቸው ተንገዳገዱ። ራቅ ብሎ አንድ ድንጋይ ታያቸው። ሄደው ቁጭ አሉበት። እንባቸውን መቆጣጠር አልቻሉም… ፈሰሰ። በጉንጫቸው ተንሸራትቶ ሱሪያቸው ላይ ተንጠባጠበ። አብረዋቸው የነበሩ ባለስልጣናት በብዙ ልመና ከተቀመጡበት አስነሷቸው። እንዳቀረቀሩ ወደ ሄሌኮኘተራቸው ገቡ። … ሄሊኮፕተሯ እንደተነሳች ተቀምጠውባት የነበረው ድንጋይ በዙ 50 ካሊበር አውቶማቲክ መሳሪያ ፍርክስክሷ ወጣ። "ነው እንዴ…? አሉ መንግስቱ ሀይለማሪያም!! "ይሄ ፈፅሞ የጠላት ጥይት አይደለም። የጄኔራል ገዝሙ ስራ ናት!!" ተስፋ መቁረጥ በደማቸው ተሰነቀረ። ከዚህ ቡሃላ የግል ህይወታቸውን ማትረፍ መሆኑ ቁልጭ ብሎ ታያቸው። ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ። በሚቀጥለው ቀን ጧት ወደ ዚምባብዌ የሚበር ቻርተር አውሮፕላን አዘዙ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አርብ ሚያዚያ 11/1983 ኮ/ል መንግስቱ ሀይለማሪያም፣ ብሄራዊ ሸንጎ የተባለውን አካል አስቸኳይ ስብሰባ ጠሩ። በዚህ ስብሰባ ማጠቃለያ ላይ የሀረሩ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ንግግር ቆሽቴያቸውን አሳረረው… "…ክቡር ኘሬዝዳንት፣ በዚህ አዳራሽ ዳግም የምንገናኝ አይመስለኝም፣ … እርስዎም 50 ሚልዮኑን የኢትዮጲያን ህዝብ በደም ባህር ማግደው፣ ቆስቁሰው… ለእሳት ዳርገው።… የቴዎድሮስን ፅዋ ከመጠጣት በቀር ሌላ የለዎትም። ይሄን እንዳማያበላሹትም አምናለው…! ይሸሻሉ የሚል እምነት የለኝም። እግዚአብሄር ምስክሬ ነው! መንጌ! እዚያችው እተቀመጡባት ወንበርዎ ላይ ቋንጣ ሆነው እንደሚቀሩ አምናለው። እግዚአብሄር ምስክሬ ነው! ይህን ባያደርጉ ግን ታሪክ ይፋረድዎታል። ኮሎኔል መንግስቱ ለጳጳሱ በሆዳቸው መልስ ሰጡ። "ወይኔ መንጌ፣ እንዲህ ልደፈር? የማን አባቱ ቀልቃላ ደብተራ ነው? እስኪ ያማከርኩት አይመስልም? ቴዎድሮስ ራሱን ያጠፋው በዘመኑ አይሮኘላን ስላልነበረ መሆኑን መረዳት እንዴት ያቅትሃል? ወዳጄ ለዚህ ልግምተኛ ህዝብ ብዬ ትርጉም አልባ ሞት እንድሞት ያምርሃል? በፍፁም አልሞትም!!" …ኮ/ል መንግስቱ ከስብሰባው ቡሃላ ወደ ቤተመንግስት ቤታቸው አመሩ። ባለቤታቸው ወይዘሮ ውባንቺና ልጆቻቸው ቅዝዝ ብለው ተቀምጠው ደረሱ። … በተቀመጡበት የሳቸውን መምጣት ሲያዩ ነቃ ነቃ አሉ። አምባሳደር አስራት ሀይሌም ነበሩ። መንግስቱ የተለመደውን ሰላምታ ሰጥተው ወደ መልበሻ ክፈላቸው አመሩ። ልብሳቸውን ቀይረው ከተመለሱ ቡሃላ ሶፋው ላይ በትካዜ ተቀመጡ። አሁን የድሮው ወሬ አልነበረም። የቤቱ ድባብ ያስፈራል። አምባሳደሩ አንዳች ነገር መናገር የፈለጉ ይመስላሉ። መንግስቱ ለመስማት ፍቃደኛ አልነበሩም። ለውጦቹን አንድ በአንድ እያነሱ መጣል ጀመሩ። በበታቾቻቸው መደፈራቸው፣ የሚያምኑት የሚታዘዛቸው ሰው መጥፋት… " ወይኔ መንጌ መጨረሻዬ ይህ ሆነ! ግንፍል ብሎ የመጣ እንባ ተናነቃቸው። …ከሁሉ ከሁሉ የነደዳቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በመፈንቅለ መንግስት ተይዘው የነበሩ ጄነራሎች መረሸን መቃወምና፣ የሳቸውንም ፎቶ ማቃጠላቸውን ሲሰሙ ነበር። መረጃውን ያደረሱላቸውን ኮ/ል ተስፋዬ ወልደስላሴ ነበሩ። "ይሄ መንጋ ተሽካላ… የድሃ ልጅ!! ብስጭት አሉ። "እሱ ተምሮ ሀገር ሊቀይር? ምን ያድርግ ያጠገብኩት እኔ!! እናቱ አሳይታው የማታውቀውን ምግብ ሲውጥ እንዴት አይጥገብ?" መንጋ ያላዩ ልጅ ሁላ!!" መንግስቱ በስሜት ተውጠው ስልክ አነሱ። ለኢሰፓ አንደኛ ተጠሪ ሻለቃ እንዳለ ተሰማ ደወሉ። "ጓድ!! ረብሻ ያነሱ ቀንደኛ ተማሪዎችን አጣርታችሁ በሁለት ቀናት ውስጥ እርምጃ ትወስዳላችሁ።"ስልኩን ዘጉት። በሶስተኛው ቀን እነዚሁ ባለስልጣናት ተመልሰው መንግስቱ ቢሮ መጡ። ቀንደኛ የተባሉትን 25 ተማሪዎች፣ ስም ዝርዝራቸውን አቀረቡ። መንግስቱ የተማሪዎቹን ስም የያዘውን ወረቀት በአይናቸው ከመረመሩ ቡሃላ "የማጣራት ሂደቱን ከጨረሳችሁ ጓድ ተስፋዬ ትቀጥላህ!! ባለፈው እንደተነጋርነው እርምጃ ትወስድባቸዋለህ። "የእጃቸውን ትሰጣቸዋለህ!! ማለት ነው። ባለስልጣናቱን አሰናበቱ። ቀጥለው ቢሮቸው የገበቱ ኮ/ል ፍሰሃ ደስታና ኮ/ል ተካ ቱሉ ነበሩ። መንግስቱ ካቀረቀሩበት ቀና ብለው አዮዋቸው። …የውድቀት ዜና አምጥተው ይሆን? ምንም ይሁን ግድ አልነበሯቸውም። ምን ያልወደቀ ነገር አለና? አድሜ ለዚህ መንጋ በርሜል…ሁሉ "ኮ/ል ፍሰሃ የመጡበትን መናገር ቀጠሉ…"ጓድ መንግስቱ፣ አንድ ነገር ልንለምንህ ነው አመጣጣችን ትላንት ጄኔራሎቹን ገደልን፣ በዚህ በተከበብንበት ወቅት፣ ለጋ ተማሪዎችን ብንገድል ህዝብ ምን ይለናል?…ባይሆን እንደ አባት መክረን ዘክረ… መንግስቱ አላስጨረሱትም ድንገት ቱግ አሉ…" አጣርታችሁ እርምጃ ውስዱ አልኩ እንጂ… መች ይገደሉ አልኩ? ቆይ ምንድነው ነገሩ? ብብቴ ስር እየተሴረብኝ ያለው ሴራ? ጠረጴዛውን በቡጢ ነረቱት… "ጓድ እንደሱ ከሆነ ችግር የለም። ለደህንነትዎ አስበን ነው። ብለው ኩምሽሽ እንዳሉ ተያይዘው ከቢሮ ወጡ።" ጊዜው በሮ የግንቦት ወር ገባ። … ከሎኔል መንግስቱ ከዚህ ቡሃላ አንድ ታላቅ ዘመቻ ወጠኑ። በሳቸው የሚመራ ሰራዊት አከማቹ። ማዘዣ ጣቢያው ከሪሙ ላይ አቆሙ። በመሃል ለአስቸኳይ ስራ፣ አሰብ ደርሰው ከቀናት ቡሃላ ሲመለሱ ከሪሙ ያዘጋጁት ጦር በቦታው አልነበረም። ተበሳጭተው ወደ አዲስ አበባ አቀኑ። ሌላ አስደንጋጭ ዜና ጠበቃቸው። የወሎው ማዘዣ ጣቢያ ነቅሎ ደብረብርሃን ሰፍሯል። ቢሆንም በፊት እሳቸው ሳያውቁት አይሞከርም ነበር። የኢአዴግ ሰራዊት የአንቦን ከተማ ለሁለተኛ ጊዜ ተቆጣጥሮ… ወደ አዲስ አበባ ለመግባት ጉዞ ጀምረዋል። መንግስቱ ይህን ጉዞ ለመግታት አንድ ታላቅ ጦርነት ለማንሳት ተነሱ። ሁኔታዉን ለመረዳ በሄሊኮፕተር አንድ ኮረብታ ላይ አረፉ። ወርደው ቁልቁል ተመለከቱ። ሠራዊታቸው ወደ አዲስ አበባ ይተማል። አስራ ሰባት አመት ሙሉ ያቆሙት እልፍኝ ሲፈርስ… ፍርስርስ ማለቱን ውስጣቸው ቁልጭ አድርጎ ነገራቸው። ወይኔ መንጌ መጨረሻዬ ይህ ሆነ? ለደቂቃዎች በዝምታ ተዋጡ። እንጥላቸው ዱብ… ሀሞታቸው ፍስስ… ቅልጥማቸው ድቅቅ… ወገባቸው ዛለ… ጉልበት ከድቷቸው ተንገዳገዱ። ራቅ ብሎ አንድ ድንጋይ ታያቸው። ሄደው ቁጭ አሉበት። እንባቸውን መቆጣጠር አልቻሉም… ፈሰሰ። በጉንጫቸው ተንሸራትቶ ሱሪያቸው ላይ ተንጠባጠበ። አብረዋቸው የነበሩ ባለስልጣናት በብዙ ልመና ከተቀመጡበት አስነሷቸው። እንዳቀረቀሩ ወደ ሄሌኮኘተራቸው ገቡ። … ሄሊኮፕተሯ እንደተነሳች ተቀምጠውባት የነበረው ድንጋይ በዙ 50 ካሊበር መሳሪያ… ድው!?… ፍርክስክሷ ወጣ። "ነው እንዴ…? አሉ መንግስቱ ሀይለማሪያም!! ሽቅብ ይዛቸው በምትወጣው ሄሊኮፕተር መስታወት ቁልቁል እያዩ … "ይሄ ፈፅሞ የጠላት ጥይት አይደለም። የጄኔራል ገዝሙ ስራ ናት!!" አሉ። ተስፋ መቁረጥ በደማቸው ተሰነቀረ። ከዚህ ቡሃላ ጥያቄው የግል ህይወታቸውን ማትረፍ መሆኑ ቁልጭ ብሎ ታያቸው። ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ። በሚቀጥለው ቀን ጧት ወደ ዚምባብዌ የሚበር ቻርተር አውሮፕላን አዘዙ። ወ/ ሮ ውባንቺና ልጆቻቸው ጓዝ ጥቅለላ ይጣደፋሉ። አምባሳደር አስራት የመንግስቱን ዋና ዋና ንብረቶች ያዘጋጃሉ። መንግስቱ ጥድፊያቸውን ያላዩ መስለው አለፏቸው። ጥቁር ገፃቸው ከሰል መስሏል። የቤተመንግስት ምግብ አብሳይ ሴቶች እየሰሟቸው ምፅ! ብለው ከንፈር ይመጣሉ። ከሁሉም የመረራቸው ይኸው የሰዉ የሀዘኔታ አተያይ ነበር። ከቁርስ ቡሃላ አራት ጠባቂዎቻቸውንና ሻለቃ ደመቀ ባንጃውን አስከትለው በሁለት ሽፍን መኪናዎች ተሳፍረው በ10ኛው በር በኩል ወጡ፣ ወደ ቦሌ። በመኪናው ጥቁር መስታወት አሻግረው ወደ ውጪ ተመለከቱ። አዲስ አበባ በቁሟ አንቀላፍታለች። ከግንባር ሸሽቶ የመጣው ሰራዊት ጠመንጃዉን ያለ ወጉ ይዞ ከልተም ከልተም ይላል። ሰዎች እየከበቡ በጥያቄ አሳራቸውን ያበለሏቸዋል። "መንጋ አዛባ … ቂጡን ቆልፎ አይዋጋ ይሸሻል። ይኸው ለዚህ ውርደት አበቃኝ። እስቲ ኢትዮጲያ የኔ ሀገር ብቻ እንደሆነች ይረከባት። ይሄ ወረኛ ህዝብ እንደ አለት ተጋግሮ ዝም ያለው እኔ ብቻ የምጎዳ መስሎት ከሆነ ይቅመሰው። … አስጎንብሶ በጉማሬ ሲዠልጠው ያኔ መንጌ መንጌ ይላል!!ኢትዮጲያን ፈርሞ አስረክቦኛል እንዴ?"! መኪናዎቹ ተከታትለው ወደ ቦሌ አየር ማረፊያ ገቡ… ምንጭ ፣= (የቄሳር እንባ (ሀብታሙ አለባቸው) ነው።) ወገሬት!!

No comments:

Post a Comment